ስኬት
ሰዓሊ ወርቅነህ በዙ፤ በሥነ ጥበቡ ሕይወት ስኬታማ መሆኑን ይገልጣል።
ያም ሊሆን የቻለው "በትክክል የሚያስተምሩ መምህራኖችን ማግኘቴና በትክክል ጥበበን መግለፅ መቻሌ የመጀመሪያው ሲሆን፤ ሁለተኛው ላለፉት 20 ዓመታት የሙሉ ጊዜ አርቲስት ሆኔ መሥራት መቻሌ ነው" ሲል ያስረዳል።
ይህም "ጥበቡን አንድ ከፍ ያለ ደረጃ ላይ አድርሽያለሁ ማለት ነው" ሲልም የጥበብ በረከት አስተዋፅዖ እሳቤውን አመላክቷል።
'Dream of Saints' by Artist Workneh Bezu. Credit: Workneh Bezu
Credit: Workbeh Bezu
ሰሞኑንም በኒው ዮርክ በተዘጋጀ ሲምፖዚየም የጥበብ ሥራዎችን አቅርቧል።
ሽልማትም አግኝቶበታል።
Credit: W.Bezu
ከቅርብ ጊዜ የወርቅነህ ውጥኖች አንዱ የስዕል ሥራዎቹን ፖርቱጋል ውስጥ ላለ አንድ ስቱዲዮ ለማቅረብ ስምምነት ላይ መድረሱ ነው።
የረጅም ጊዜ ትልሞቹ አንድ የግል ጋለሪ ማቋቋምና ታዳጊ የጥበብ ሰዎች ሕዝብና አገር ከቸሩት ትሩፋት ማጋራት ነው።
Credit: Workneh Bezu