አንጋፋው አርቲስት ሰለሞን ዓለሙ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አንጋፋው ፀሐፌ ተውኔት፣ አዘጋጅ እና ተዋናይ ሰለሞን ዓለሙ በብዙዎች ዘንድ በ"አብዬ ዘርጋው" የሬዲዮ ድራማ ይበልጥ ይታወቃል።

News

Artist Solomon Alemu. Source: PR

ሰለሞን ዓለሙ በ5 ቋንቋዎች ከ500 በላይ የሬዲዮ ድራማዎችን፣ የመድረክ ቴአትሮችን እና መነባንቦችን አዘጋጅቷል።

በተለይም ከዳንኪራው ጀርባ፣ ፍራሽ ሜዳ፣ ገመዱ እና አዙሪትን የመሳሰሉ ተወዳጅ ስራዎችን እንዳበረከተ ወዳጆቹ ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ ሬዲዮ ታሪክ በተለይ ከ1975-1980 ገናና ስራዎችን ያበረከተበት ወርቃማ ዘመኑ ነበር።

ሰለሞን በቅርቡ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ትናንት ሌሊቱን ከዚህ ዓለም ተለይቷል።


Share
Published 28 June 2022 6:02pm
By Stringer Report

Share this with family and friends