የ DSTV ሚዲያ ትዕይንት በምናባዊ እግር ኳስ ውድድርና በ "አደይ ፋሽን ሾው" ታጅቦ ቀረበ

ጥቅምት 4 ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሚዲያ አመራሮች ፧ የስፖርት እና የፊልም ጥበብ ዝነኞች በተገኙበት ዓመታዊው ባለ ዘርፈ ብዙ ምርጫ (DSTV) ሚዲያ ሾውኬዝ 2022 በተለያዩ ዝግጅቶች ታጅቦ በድምቀት ተከናውኗል።

Virtual Football.jpg

Virtual Football. Credit: D.Kebede

የመልቲቾይዝ ኢትዮጵያ የሬጉላቶሪና ኮርፖሬት ጉዳዮች ኃላፊ አቶ መታሰቢያ በላይነህ በእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸው እንዳሉት “መልቲቾይዝ (DSTV) በኢትዮጵያ ስፖርት፣ ባሕልና መዝናኛ ዘርፎች እያከናወነ ያለውን ኢንቨስትመንት አጠናክሮ ይቀጥላል” ብለዋል።

ይህ ዓመታዊ የሚዲያ ሾውኬዝም ዲኤስቲቪ በስራ ዕድል ፈጠራ ፧ በባህል፣ ስፖርትና ሀገራዊ ይዘቶች አቅርቦት፣ በሀገር ገፅታ ግንባታ ብሎም በቴክኖሎጂ እውቀት ሽግግር እያደረገ ያለውን ጉልህ አስዋጽዖ ለማሳየት ዓላማ ያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

Metasebia Belayneh.jpg
Metasebia Belayneh. Credit: D.Kebede

አቶ መታሰቢያ አክለውም በቅርቡ በኬንያ ናይሮቢ በተከናወነው የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የፊልም ጥበብ ተማሪዎች ምርቃት ስነ ስርዓት ኢትዮጵያዊው መልካሙ ኃይሌ ከመልቲቾይስ ታለንት ፋክተሪ አካዳሚ ምሩቃን መካከል አንደኛ በመውጣት ወደ ኒዮርክ ፊልም አካዳሚ የሚያኬደውን ከፍተኛ ሽልማት ማሸነፉ አውስተው፤ መልቲቾይስ ታለንት ፋክተሪ ለአንድ ዓመት ለወጣት የፊልም ባለሙያዎች በንድፈሀሳብና በተግባር ትምህርት የሚሰጥ የአንድ ዓመት ስኮላርሽፕ ሲሆን በዓመቱ መጨረሻም ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ምሩቃን ወደ ኒውዮርክ፣ ቦሊውድና ደቡብ አፍሪካ ለላቀ ከፍተኛ ትምህርት የሚጓዙበትን ሽልማት ያሸንፋሉ፤ ልጃችን መልካሙ ኢትዮጵያ ወክሎ በከፍተኛ ውጤት በማሸነፉ ለላቀ ትምህርት ወደ ኒውዮርክ እንደሚጓዝ” ተናግረዋል፡፡

የመልቲቾይዝ አፍሪካ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ፍልህሉ ባዱጌላ ከደቡብ አፍሪካ በቪዲዮ ባስተላለፉት የመክፈቻ መልዕክት “ የአፍሪካን ታሪክና ባህል በመተረክና በስፖርትና መዝናኛ ይዘቶች አቅርቦት ረገድ ከእስካሁኑ በበለጠ እንደሚሰሩ ገልፀው፤ በተለይ ለቀጣዩ የዓለም ዋንጫ ስርጭት ከፍተኛ ዝግጅት መደረጉን” አውስተዋል፡፡

የመክፈቻ ንግግር የክብር እንግዳው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ እድሪስ “ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ለኢትዮጵያውያን ትኩረት ያደረጉ የቴሌቪዥን ቻነሎችን ይፋ ያደረገው ዲኤስቲቪ በአጭር ጊዜ ውስጥ የመንግስት ትውልድና ሀገርን የመገንባት ኃላፊነትን በማገዝ ረገድ ሃላፊነቱ እየተወጣ ያለ ተቋም ነው” ሲሉ ገልፀዋል፡፡

Mohammed Idris.jpg
Mohammed Idris. Credit: D.Kebede
ሌላኛው የክብር እንግዳ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታው አምባሳደር መስፍን ቸርነት በበኩላቸው “ኢትዮጵያዊ ይዘቶችን በማጉላት የኢትዮጵያ ባህሎችን እና እሴቶችን የጠበቁ ድራማዎችንና ፊልሞችን ለኢትዮጵያውያውንና በውጭው ዓለም ላሉ ተመልካቾች እንዲተላፉ እያደረገ መሆኑ የሚያስመስግነው ነው” ብለዋል፡፡

Ambassador Mesfin Cherinet.jpg
Ambassador Mesfin Cherinet. Credit: D.Kebede
በሚዲያ ሾውኬዙ መጪውን እና ተናፈቂውን የዓለም ዋንጫን ጨምሮ በሱፐርስፖርት የሚተላለፉትን የአውሮፓ ተወዳጅ ሊጐች እና የኢትዮጵጵያ ፕሪምየር ሊግ የሚዘክር የቨርቹዋል የእግር ኳስ ውድድር ታዳሚዎች አድርገዋል። ሽልማትም ተበርክቷል፡፡

ባልተለመደ መልኩ የቀረበውና በታዳሚዎች ዘንድ አድናቆት የተቸረው የ”አደይ ፋሽን ሾው”ም ቀርቧል። በአቦል ቴሌቪዥን በየዕለቱ የሚተላለፈውን የአደይ ድራማ ገጸ በህሪያት አልባስትን ዲዛይኖች በምታዘጋጀው ዲዛይነር ዳግማዊት ተስፋዬ ዲዛይን የተደረጉና በድራማው ጥቅም ላይ የዋሉ የኢትዮጵያ ባህል አልባሳት በዘመናዊ መልክ ተዘጋጅተው በመድረኩ ቀርበዋል፡፡

Fashion Show.jpg
Adey Fashion Show. Credit: D.Kebede

ወጣቱ ተወዳጅ ድምጻዊ እሱባለው ይታየው በመሀሪ ብራዘርስ ባንድ ታጅቦ አደይ የተሰኘውን የተከታታይ ድራማው ማጀቢያ ሙዚቃውን በድንቅ ብቃት አቅርቦ ታዳሚውን ያዝናና ሲሆን በአቦል ቴሌቪዥን የሚቀርበው የ”ሚዩዚኮሎጅ” የሙዚቃ ሾው አዘጋጁ ሔኖክ መሐሪም ተወዳጅ ሙዚቃውን በመድረኩ ተጫውቷል፡፡

የአደይ ድራማ ተዋናዮቹ በእምነት ሙሉጌታ (አደይ) እና ሰርካለም ጌታሁን (ሮማን) በየዕለቱ በሚከናወነው የድራማው የፕሮዳክሽን ቀረፃ እንዲሁም የትወና ጥበብ ልምዳቸውን ያካፈሉ ሲሆን የአላቲኖስ ፊልም ሰሪዎች ማህበር ፕሬዝደንቱ ምኒልክ መርዕድ “አደይ ድራማ በቀረፃና ይዘት የተዋጣለትና በአዳዲስ ቴክኖኮችም የታገዘ ነው” ሲል ሙያዊ አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡

DSTV.jpg
MS - 2022. Credit: D.Kebede
በሌላ መልኩ በሀገራዊ ይዘትነቱና በሸንቋጭነቱ በተመልካቾች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈው “አስኳላ” ሲትኮም ፕሮዲዩሰር በኃይሉ ዋሴ (ዋጄ)እና የሲትኮሙ ተዋናዮች ደመወዝ ጎሽሜ (የኔታ) እና ሚካኤል ታምሬ በሚዲያ ሾውኬዙ ልምዳቸውን ያገሩ አርስቲቶች ናቸው፡፡ አርቲስቶቹ “አስኳላ በአቦል ቴሌቪዥን ለሁለት ዓመት የሚጠጋ ጊዜ እየተላለፈ ያለና በትምህርት ስርዓቱ ላይ ሲስተዋሉ የነበሩ እንከኖችን እያዋዛ ሲያሳይ መቆየቱን በዚህም አድናቆት እያገኙበት” መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በመድረኩ ልምዳቸውን ያጋሩት አርቲስቶቹ ዲኤስቲቪ ለኢትዮጵያ ፊልም ዕድገት በፋይናንስና በሚዲያ ስርጭት እያደረገ ያለው አስተዋፅኦ የሚደነቅና ሌሎችም ሊከተሉት የሚገባ ነው ተናግረዋል፡፡

DSTV2.jpg
MS - 2022. Credit: D.Kebede
በሚዲያ ሾውኬዙ ከተጋበዙት የክብር እንግዶች አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን (ዋሊያዎቹ) ዋና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ “ግብፅን ያህል ታላቅ ቡድን ማሸነፍ የቻልነው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በመጠናከሩ ነው” ያለ ሲሆን “ ለዚህ ደግሞ ሱፐርስፖርት/ዲኤስቲቪ በስርጭትና በፋይናንስ ክለቦቹን ማገዙ ትልቅ ሚና አለው” ብሏል፡፡

የሊጎች መጠናከር ለሀገራት ብሔራዊ ቡድኖች ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው የገለፀው ዋና አሰልጣኝ ውበቱ ሱፐርስፖርት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ እያበረከተ ያለውን ሁለንተናዊ አስተዋፅኦ አጠናክሮ እንዲቀጥልም እምነቱን ተናግሯል፡፡

በሾውኬዙ ከሱፐርስፖርት ጋር በመስራት ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የስፖርት ተንታኞችና የፕሮዳክሽን ባለሙዎች ልምድም በዶክመንተሪ ፊልም ቀርቧል፡፡

DSTV3.jpg
MS - 2022. Credit: D.Kebede

በየዓመቱ የሚከናወነው የመልቲቾይስ ዓመታዊ የሚዲያ ሾውኬዝ በሁሉም የአፍሪካ አገራት የሚከናወን ሲሆን በኢትዮጵያም በየዓመቱ ጥቅምት መጀመሪያ ይከናወናል፡፡ መልቲቾይስ አፍሪካ “ሱፐርስፖርት፣ ዲኤስቲቪ፣ ኤም-ኔት እና ኤርዴቶ” የተሰኙ ታላላቅ ኩባንያዎችን በስሩ ያቀፈ የአፍሪካ ግዙፉ የስፖርትና መዝናኛ ይዘቶች አቅራቢ ሲሆን በ50 የአፍሪካ አገራት እየሰራ ይገኛል፡፡

Share
Published 15 October 2022 11:17pm
By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends